Fana: At a Speed of Life!

የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ ምሽት ይደረጋል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ፖርቹጋል ከስፔን ዛሬ ምሽት የሚያደርጉት የፍጻሜ ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል፡፡

ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሙኒክ አሊያንዝ አሬና ስታዲየም የሚደረግ ሲሆን÷ ሁለቱ ቡድኖች ካላቸው ምርጥ ተጫዋቾች አንጻር አጓጊ ሆኗል፡፡

በፖርቹጋል በኩል የ40 ዓመቱ ክሪስቲያኖ ሮናልዶን ጨምሮ ቪቲኒሃ፣ ጆዓዖ ኔቬስ የመሳሰሉ ከዋክብቶች የሚያደርጉት እንቅስቃሴ የሚጠበቅ ሲሆን÷ በስፔን በኩል የባርሴሎና ኮከቦች ላሚንያማል፣ ፔድሪን የመሳሳሉ ተጫዋቾች ይጠበቃሉ፡፡

በኔሽንስ ሊጉ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ፖርቹጋል ጀርመንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜው ማለፍ ስትችል÷ ስፔን በበኩሏ ፈረንሳይን 5 ለ 4 በሆነ ውጤት አሸንፋ ነው የፈጻሜ ተፋላሚ የሆነችው፡፡

ቀን 10 ሰዓት ላይ ጀርመን እና ፈረንሳይ 3ኛ ደረጃን ይዘው ለማጠናቀቅ ይፋለማሉ፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.