ሪያል ማድሪድ ዲን ሁይሰንን አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ የመሐል ተከላካይ ስፍራ ተጫዋች የሆነውን ዲን ሁይሰንን ከቦርንማውዝ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
ስፔናዊው ተጫዋቹ በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን በእንግሊዙ ክለብ ቦርንማውዝ በነበረው ቆይታ በሊጉ 32 ጨዋታዎችን አድርጎ ሦስት ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን፤ ሁለት ግብ የሆኑ ኳሶችንም አመቻችቶ አቀብሏል፡፡
የ20 ዓመት ወጣቱ የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ዲን ሁይሰን ከቦርንማውዝ አስቀድሞ የጣሊያን ክለቦች በሆኑ ሮማ እና ጁቬንቱስ መጫወቱ ይታወሳል፡፡
በዛሬው የትውውቅ ፕሮግራም ላይ የክለቡ ፕሬዚዳንት ፍሎረንቲኖ ፔሬዝ አዲሱ ፈራሚያቸውን እንኳን ደህና መጣህ ብለው አቀባበል አድርገውለታል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!