Fana: At a Speed of Life!

ሪያል ማድሪድ ዲን ሁይሰንን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ የመሐል ተከላካይ ስፍራ ተጫዋች የሆነውን ዲን ሁይሰንን ከቦርንማውዝ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

ስፔናዊው ተጫዋቹ በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን በእንግሊዙ ክለብ ቦርንማውዝ በነበረው ቆይታ በሊጉ 32 ጨዋታዎችን አድርጎ ሦስት ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን፤ ሁለት ግብ የሆኑ ኳሶችንም አመቻችቶ አቀብሏል፡፡

የ20 ዓመት ወጣቱ የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ዲን ሁይሰን ከቦርንማውዝ አስቀድሞ የጣሊያን ክለቦች በሆኑ ሮማ እና ጁቬንቱስ መጫወቱ ይታወሳል፡፡

በዛሬው የትውውቅ ፕሮግራም ላይ የክለቡ ፕሬዚዳንት ፍሎረንቲኖ ፔሬዝ አዲሱ ፈራሚያቸውን እንኳን ደህና መጣህ ብለው አቀባበል አድርገውለታል።

 

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.