Fana: At a Speed of Life!

የጎርፍ አደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የክልሎችን አቅም በማጠናከር የክረምት ጎርፍ አደጋ ተጋላጭነትን ለመቀነስ እየሰራሁ ነው አለ።

የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ሽፈራሁ ተክለማርያም (ዶ/ር) ከክልሎች ጋር ለጎርፍ አደጋ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ስራ በቅንጅት መሰራቱን ገልጸዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባለፈው ዓመት በጎርፍና መሬት ናዳ የተፈናቀሉ ዜጎችን ዳግም የማቋቋም ስራ ባለፉት 10 ወራት ከመስራት በተጨማሪ የቅድመ መከላከል ተግባር እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽነር ጋንታ ጋማ ተናግረዋል።

ቀሪዎቹን የጎርፍና የመሬት ናዳ ተጎጂዎች የሰኔ ወር ሳይጠናቀቅ ወደ ሌላ ቦታ የማስፈር ስራ መከናወኑ እንደሚቀጥልም ገልጸዋል።

የአማራ ክልል በበጋ ወራት 145 ሚሊየን ብር ወጪ በማድረግ የጎርፍ ቅድመ መከላከል ስራ መከናውኑን የገለጹት ደግሞ በክልሉ አደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን የቅድመ ማስጠንቀቂያና ምላሽ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ዘውዱ ናቸው።

በክልሉ ለጎርፍ ተጋላጭ የሆኑ 33 ወረዳዎችን በመለየት ህብረተሰቡን ያሳተፈ ቅድመ ዝግጅት ስራ መሰራቱንም ጠቁመዋል።

በእዮናዳብ አንዷለም

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.