Fana: At a Speed of Life!

የፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ 7 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የፊንጫአ ስኳር ፋብሪካ በ2017 በጀት ዓመት የስኳር እና ኢታኖል ምርት ለገበያ በማቅረብ 7 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ።

ፋብሪካው ዓመታዊ የስኳር ምርቱን 2 ነጥብ 7 ሚሊየን ኩንታል እንዲሁም የኢታኖል ምርቱን 20 ሚሊየን ሊትር ለማድረስ አቅዶ እየሰራ እንደሆነ አስታውቋል።

የፋብሪካው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ መንግስቱ ኃይለማርያም ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደተናገሩት፤ ፋብሪካው የማምረት አቅሙን ለማሳደግ የሚያስችሉ ማሽኖችን እየተከለ ይገኛል።

በተያዘው በጀት ዓመት 383 ሺህ ኩንታል ስኳር እንዲሁም 4 ነጥብ 7 ሚሊየን ሊትር ኢታኖል ያመረተው ፋብሪካው፤ ምርቱን ለገበያ በማቅረብ 7 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር አግኝቷል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት 19 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ አገዳ መተከሉን ገልጸው፤ ይህንን አቅም ወደ 21 ሺህ ሄክታር ከፍ ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነም ተናግረዋል።

ፋብሪካው በተለያየ ምክንያት ጉዳት በማስተናገዱ ለማገገም ስትራተጂክ ዕቅድ ነድፎ ምርታማነቱን ለማሳደግ እየሰራ ነው ብለዋል።

መንግስት ስኳር ፋብሪካዎች ራስ ገዝ እንዲሆኑ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረትም ከስኳር እና ኢታኖል ምርት ባሻገር በግብርና ዘርፍ በመሰማራት የገቢ ማሳደግ እና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የማድረግ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል።

ፋብሪካዎች ራስ ገዝ እንዲሆኑ መወሰኑ የማምረት አቅምን በማሳደግ ትርፋማ የሚያደርግ መሆኑን ዋና አስኪያጁ ገልጿል።

በገላና ተስፋ

 

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

 

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.