በኖርወይ ኦስሎ ዳይመንድ ሊግ አትሌት የኔዋ ንብረት አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኖርዌይ ኦስሎ በተካሄደው የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ዳይመንድ ሊግ ውድድር አትሌት የኔዋ ንብረት አሸንፋለች።
አትሌት የኔዋ በ30 ደቂቃ 28 ሰከንድ ከ82 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ነው ቀዳሚ የሆነችው፡፡
አትሌት ጫልቱ ዲዳ በበኩሏ በ30 ደቂቃ 33 ሰከንድ ከ86 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት 3ኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቅቃለች፡፡