Fana: At a Speed of Life!

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት 2 ሺህ 500 ቤቶችን ለመገንባት አቅደናል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2017 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት 2 ሺህ 500 ቤቶችን ለመገንባት እቅድ ይዘናል አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።

የከተማ አስተዳደሩ የዘንድሮ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የመክፈቻ መርሐ ግብር ላይ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንዳሉት፤ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ባህል ሆኖ መቀጠል ያለበት መልካም ተግባር ነው።

በለውጡ ዓመታት በከተማዋ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችንና ባለሃብቶችን በማስተባበር የበጎ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን ጠቅሰው፤ ዘንድሮም በርካታ ሰው ተኮር ተግባራት እንደሚፈጸሙ አረጋግጠዋል።

18 የተለያዩ በጎ ፈቃድ ተግባሮችን ለመተግበር መታቀዱን ጠቅሰው፤ በመርሐ ግብሩ 2 ሺህ 500 ቤቶችን በ90 ቀናት ለመገንባት መታቀዱን ገልጸዋል።

በተጨማሪም 500 ሺህ የሚሆኑ ለከተማዋ ነዋሪዎች በድግግሞሽ ማዕድ የማጋራት ዕቅድ መያዙንም አመልክተዋል።

በነፃነት ፀጋይ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.