ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የኢትዮጵያ ቡናን የማሸነፊያ ግቦች ዲቫይን ዋቹኩዋ እና አማኑኤል አድማሱ አስቆጥረዋል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና በ59 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ45 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
ኢትዮጵያ ቡና ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል ሲመለስ ቅዱስ ጊዮርጊስ በበኩሉ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም፡፡
የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሻምፒዮኑ ኢትዮጵያ መድን ከ ሀድያ ሆሳዕና ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!