Fana: At a Speed of Life!

የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በባህር ዳር የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ፣ ምክትል ጠቅላይ ማኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በባህር ዳር ከተማ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ።

በጉብኝቱ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሙዓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ የማዕድን ሚኒስትር ሃብታሙ ተገኝ (ኢ/ር) እና ሌሎች የከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

ባህርዳር ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቹ÷ በዓባይ ወንዝ ላይ የተገነባውን ድልድይ እና የጣና ሐይቅ ዙሪያ እየተሰራ ያለውን የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ተመልክተዋል።

በባህርዳር የኮሪደር ልማት ሥራ በመሥራት የጣና ሐይቅን ከከተማዋ ጋር የማስተሳሰር ሥራ እየተሰራ መሆኑ ይታወቃል።

በዚህም የከተማዋ ነዋሪዎች በውስን ስፍራዎች ብቻ የነበራቸውን ትስስር በማስፋት በሐይቁ አምስት አቅጣጫዎች በተሰራው ልማት ሐይቁ ለከተማዋ ያለውን አበርክቶ ለማስፋት እየተሰራ ነው።

በባህርዳር ከተማ የተሰራው ዘመናዊ ድልድይ በከተማዋ ያለውን የትራፊክ እንቅስቃሴ ከማቀላጠፍ ባለፈ ለቱሪዝም እና መሰል የከተማዋ ልማቶች ልዩ አበርክቶ አለው።

በለይኩን ዓለም

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.