Fana: At a Speed of Life!

በአማራ ክልል የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን ለማዘመን እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል የገቢ አሰባሰብ ሥርዓቱን ለማሳደግና ለማዘመን በትኩረት እየተሰራ ነው አለ የክልሉ ገቢዎች ቢሮ፡፡

በቢሮው የግብር ትምህርትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ታዘባቸው ጣሴ እንዳሉት÷ በበጀት ዓመቱ 71 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ ነው፡፡

ባለፉት 11 ወራት ከመደበኛና ከተማ አገልግሎት 53 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን ነው ያስረዱት፡፡

በዚህም የእቅዱን 74 ነጥብ 3 በመቶ ማሳካት መቻሉን አቶ ታዘባቸው ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

የግብር አሰባሰብ ሥርዓቱን ለማዘመንና ቀልጣፋ ለማድረግ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመተግበር ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ መከናወኑን አብራርተዋል፡፡

በክልሉ የሚስተዋለው የጸጥታ ችግር እና የግብር ሥወራ ለገቢ አሰባሰብ ሒደቱ ተግዳሮት መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በሌላ በኩል ሀሰተኛ ደረሰኝ የሚያቀርቡና ያለ ደረሰኝ አገልግሎት እና እቃ የሚሸጡ ነጋዴዎችን ለመቆጣጠር በትብብር እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

ክልሉ ያለበትን ነባራዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት ከግብር የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግና አሰባሰቡን ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላልም ነው ያሉት፡፡

በዮናስ ጌትነት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.