ፕሬዚዳንት ታዬ በአፍሪካ- አሜሪካ ቢዝነስ ጉባዔ ላይ እየተሳተፉ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአፍሪካ-አሜሪካ የቢዝነስ ጉባዔ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎችና የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በአንጎላ ሉዋንዳ በይፋ ተጀምሯል።
በጉባዔው በፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑክ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡
በመርሐ ግብሩ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች፣ ሚኒስትሮች፣ የመንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የአሜሪካ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጨምሮ 1 ሺህ 500 ተሳታፊዎች ታድመዋል፡፡
ጉባዔው በአፍሪካና በአሜሪካ መካከል ያለውን የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር በሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች ላይ ቀጣይ አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀምጥ ታምኖበታል።
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በጉባዔው ንግግር የሚያደርጉ ሲሆን÷ ከጉባዔው ጎን ለጎንም የተለያዩ የሁለትዮሽ ውይይቶችን እንደሚያካሂዱ የዘገበው ኢዜአ ነው፡፡
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!