Fana: At a Speed of Life!

በወላይታ ሶዶ በደረሰው የትራፊክ አደጋ የ3 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በወላይታ ሶዶ ከተማ በዛሬው ዕለት በደረሰው የትራፊክ አደጋ የሦስት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

የሶዶ ከተማ ፖሊስ ዋና አዛዥ ምክትል ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጹት÷ በወላይታ ሶዶ ከተማ የፍሳሽ ማስወገጃ ተሽከርካሪ ባደረሰው አደጋ እስካሁን የ3 ሰዎች ሕይወት አልፏል።

በአደጋው በሦስት ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱንና ጉዳት ከደረሰባቸው መካከል አንደኛው በአስጊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በአደጋው ህይወታቸውን ያጡት ሦስቱም ወንዶች ሲሆኑ÷ ሁለቱ በመንገድ ላይ የነበሩ የመኪና ረዳቶችና አንድ የሊስትሮ ባለሙያ መሆኑን ነው የገለጹት።

ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎችም ወደ ሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታልና ኦቶና ማስተማሪያ ሆስፒታል ለህክምና መወሰዳቸውን ጠቁመዋል።

የአደጋው መንስኤ በጉዞ ላይ የነበረ ፍሳሽ ማስወገጃ ተሽከርካሪ ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር ፍሬን ያለመስራት ችግር በማጋጠሙ እንደሆነም አንስተዋል።

በዚህም ስድስት ተሽከርካሪዎችን በመግጨት ከባድ የንብረት አደጋ መድረሱንም ነው የተናገሩት።

በማስተዋል አሰፋ

 

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.