ከመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ጋር የተደረገው ምክክር የጋራ ትርክትን ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽዖ ይኖረዋል – ምሁራን
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ከመንግስት ጋር ተቀራርበው መምከራቸው የጋራ ትርክትን በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ይኖረዋል አሉ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ምሁራን።
ውይይቱ ሀገራዊ የልማት አጀንዳዎችን የመፈጸም አቅም በማስረጃ በማስደገፍ ለማቅረብ የአሰራር ምቹነትን ለሚዲያዎች እንደሚፈጥርም ምሁራኑ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ጠቅሰዋል፡፡
በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን መምህር ደህናሰው ሽመልስ ውይይቱ በሚዲያዎች ያለው ጥንካሬና ተግዳሮት የተለየበት ነው ብለዋል፡፡
መንግስት ሙያዊ ሥነ ምግባርን ተከትለው ለሚሰሩ ሚዲያዎች ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኝነት ማሳየቱንም አድንቀዋል፡፡
በወልድያ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠንነትና ኮሙኒኬሽን መምህሩ ሀብታሙ ሙሉጌታ በበኩላቸው÷ ውይይቱ የሀገር ጥቅምና የሚዲያ ነጻነትን በተንተራሰ መልኩ ለመዘገብ ይበልጥ ግልጽነት የሰጠ ነው ብለዋል፡፡
ውይይቱ ተቀራራቢ ሀገራዊ ትርክት ለመፍጠር የጎላ ሚና እንዳለውም ነው የጠቆሙት።
በእዮናዳብ አንዱዓለም
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!