Fana: At a Speed of Life!

በብሔራዊ ሠላምና ደህንነት ላይ ያተኮረ ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የምርምርና ልማት ስራን በተሟላ መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የብሔራዊ ደህንነት ኮንፈረንና የምርምር አውደጥናት እየተካሄደ ነው።

አውደጥናት “በደህንነትና ስትራቴጂክ ጉዳዮች የሰለጠኑ ብቁ አመራሮችን በማፍራት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም እናስከብራለን” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚገኘው።

አውደጥናቱ በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ምርምርና ልማት ሥራ ላይ ያሉ መልካም አጋጣሚዎችና ተግዳሮቶች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።

በመከላከያ ሠራዊት ወታደራዊ ምርምርና ልማት ዘርፍ ላይ ያለውን ገፅታ ለመቀየርና ፈጣን ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ ስራዎች በዕቅድ መሰራት እንዳለባቸው ተጠቁሟል፡፡

የኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች በውይይቱ ወቅት እንደገለፁት፤ ተመራማሪዎች ምርምር ለማድረግ ብቃት እንዲኖራቸው የሚያስችሉ ሁኔታዎችን መፍጠር ያስፈልጋል።

የመከላከያ የምርምር ተቋማትን ትስስርና አደረጃጀት የሚያጠናክር ስርዓትም መፈጠር እንዳለበት ተነስቷል።

የብሔራዊ ደህንነት ኮንፈረንስ እና የምርምር አውደጥናቱን ያዘጋጀው የመከላከያ ዋር ኮሌጅ ነው።

በየሻምበል ምህረት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.