Fana: At a Speed of Life!

5ኛው የፋና ላምሮት የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ነገ ቀጥሎ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በየሳምንቱ ቅዳሜ ከአስገራሚ ተወዳዳሪዎች ብቃት ጋር የቀጠለው ደማቁ 5ኛው የፋና ላምሮት የአሸናፊዎች አሸናፊ የድምጻውያን ውድድር ነገም ቀጥሎ ይካሄዳል።

በውድድሩ የምድብ ሁለት ተወዳዳሪዎች እዮቤል ጸጋዬ፣ ካሳሁን ዘውዱ፣ ብሩክ ሰለሞን፣ ናሆም ነጋሽ፣ አብርሃም ማርልኝ ፣ ሱራፌል ደረጀ እና ናሆም ካሳዬ በቀጥታ ሥርጭት ይፎካከራሉ፡፡

በዕለት አቀራረብ መሰረት በሚያደርገው የፋና ላምሮት ውድድር ላይ በዳኞች እና በተመልካቾች ድምጽ በየሳምንቱ አንድ ተሰናባች ይኖራል።

በነገው 5ኛው የፋና ላምሮት የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር አንድ አንጋፋና ተወዳጅ ሙዚቀኛ በክብር እንግድነት ይታደማል።

ውድድሩን በፋና ቴሌቪዥን እና በሁሉም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች በቀጥታ ሥርጭት መከታተል ይቻላል፡፡

በአጠቃላይ ለፋና ላምሮት የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ከ3 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ ሽልማት ተዘጋጅቷል፡፡

በ13ኛው ሳምንት አራት ምርጥ ተወዳዳሪዎችን ይዞ የፍጻሜ ውድድሩን የሚያካሂደው ፋና ላምሮት የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር የዋንጫ እና የአዲስ ሙዚቃ ሽልማትንም ያበረክታል።

በለምለም ዮሐንስ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.