Fana: At a Speed of Life!

በጋምቤላ ክልል 3 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጋምቤላ ክልል ባለፉት 11 ወራት 3 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጠ፡፡

የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሎው ኡቡፕ (ዶ/ር) ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ የክልሉን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡

በተለይም አሁን ላይ በክልሉ የተፈጠረው አስተማማኝ ሰላም የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እንዲጨምር ማድረጉን ነው ያስረዱት፡፡

በበጀት ዓመቱ 11 ወራት በኢንዱስትሪ፣ በግብርና እና በአገልግሎት ዘርፎች ለመሰማራት ከ3 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ 223 ባለሃብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡

አልሚ ባለሃብቶቹ 17 ሺህ 196 ሔክታር የመስሪያ ቦታ መረከባቸውን ጠቁመው÷ ወደ ሥራ እንዲገቡ አስፈላጊው ድጋፍ እና ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡

ባለሃብቶቹ ሥራ ሲጀምሩ ለ11 ሺህ 14 ዜጎች ቋሚ እና ጊዜያዊ የሥራ እድል ይፈጥራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም አመልክተዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.