Fana: At a Speed of Life!

ምክር ቤቱ የ350 ሚሊየን ዶላር የብድር ስምምነት አጸደቀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በዓለም አቀፍ የልማት ማህበር መካከል ለሁለተኛው ዘላቂና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ልማት ፖሊሲ ማስፈጸሚያ የተደረገውን የብድር ስምምነት አዋጅ መርምሮ በሙሉ ድምጽ አጸደቀ፡፡

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ ልዩ ስብሰባውን አድርጓል፡፡

በዚሁ ወቅት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ በሰጡት ማብራሪያ፤ 350 ሚሊየን ዶላር የብድር ስምምነቱ ከወለድ ነፃ የሆነ በረዥም ጊዜ የሚከፈል ብድር ነው።

የኢትዮጵያ መንግስት ልማት ላይ ትኩረት አድርጎ የኢኮኖሚ ሪፎርሙ ላይ የሚታይ ለውጥ ማምጣቱን ተከትሎ የመጣ የብድር ስምምነት ነው ብለዋል፡፡

አጠቃላይ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያን ለማጠናከር እና ለማስፈፀም ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ እንደሆነም ተመላክቷል።

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው እጅግ በጣም ውጤታም መሆኑ ስለታመነበት ስምምነቱ ተፈፅሟል ነው ያሉት፡፡

በሚቀጥለው ዓመት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ከዘንድሮ የበለጠ ውጤት ያመጣል ሲሉም ገልፀዋል፡፡

በወንድማገኝ ጸጋዬ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.