Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል 9 ነጥብ 8 ሚሊየን ሔክታር ለዘር ዝግጁ ተደርጓል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል በመኸር እርሻ እስካሁን 9 ነጥብ 8 ሚሊየን ሔክታር መሬት ለዘር ዝግጁ ተደርጓል አለ የክልሉ ግብርና ቢሮ፡፡

የቢሮው ም/ሃላፊ አቶ በሪሶ ፈይሳ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት ÷ በክልሉ ለመኸር እርሻ አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡

በዚህ መሰረትም እስካሁን 9 ነጥብ 8 ሚሊየን ሄክታር መሬት ለዘር ዝግጁ የተደረገ ሲሆን ÷ 5 ነጥብ 4 ሚሊየን ሔክታሩ ደግሞ በዘር ተሸፍኗል ብለዋል፡፡

በመኸር እርሻ ዋና ዋና ሰብሎችን ጨምሮ የአገዳ፣ የጥራጥሬና የቅባት እህሎች እንደሚለሙ ጠቁመው÷ ከ368 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አመልክተዋል፡፡

በተመሳሳይ በአፋር ክልል በመኸር እርሻ 45 ሺህ ሔክታር በተለያዩ ሰብሎች ለመሸፈን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ የሰብል ልማት ዳይሬክተር አቶ ሃመዱ ሙሃመድ ተናግረዋል፡፡

በክልሉ በመኸር የሚለማው መሬት በየዓመቱ እየጨመረ መምጣቱን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ÷ እስካሁንም ከ28 ሺህ ሔክታር በላይ ማሳ መዘጋጀቱን ጠቅሰዋል፡፡

በቆሎ፣ ጥጥና ሱፍን ጨምሮ የተለያዩ ሰብሎች በመኸር እርሻ የሚለሙ ሲሆን÷ ከ641 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅም አብራርተዋል፡፡

በዙፋን ካሳሁን

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.