ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከሮተሪ ኢትዮጵያ አመራሮች ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከሮተሪ ኢትዮጵያ አመራሮች ጋር ትውውቅና ውይይት አድርገዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ታዬ በውይይቱ ወቅት እንዳሉት፤ ተቋሙ በስነ ምግባር፣ በጤናና በተለያየ መስክ እየሰራ ያለዉ ተግባር የሚበረታታ ነው፡፡
ይህ ስራ በሕብረተሰቡ ዘንድ የበለጠ እንዲታወቅ መሰራት እንዳለበትም ተናግረዋል፡፡