Fana: At a Speed of Life!

የአረንጓዴ አሻራ ለዘላቂ ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ነው – ተስፋዬ ቤልጂጌ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ለዘላቂ ኢኮኖሚ ግንባታ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ነው አሉ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ ቤልጂጌ (ዶ/ር) ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እና ሠራተኞች ዛሬ ሰባተኛ ዙር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አከናውነዋል።

ተስፋዬ ቤልጂጌ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ የአየር ንብረት ለውጥ በዓለም ላይ የጎርፍ፣ ድርቅ፣ የአፈር መሸርሸርን ጨምሮ ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ እንቅፋት የሚሆኑ ሳንካዎችን ፈጥሯል።

ለእነዚህና መሰል ችግሮች ምላሽ ለመስጠት ኢትዮጵያ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ተግባራዊ ባደረገችው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር 40 ቢሊየን ችግኞች መተከላቸውን ጠቅሰዋል።

በዚህም በአፍሪካም ሆነ በዓለም ምሳሌ የሚሆን ውጤት ተገኝቷል ያሉት ዋና ተጠሪ ሚኒስትሩ÷ በመርሐ ግብሩ የኢትዮጵያን ልማትና ብልጽግና ቀጣይነት የሚያረጋግጡ ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን አብራርተዋል።

በሀገር ደረጃ የሚተከሉ ችግኞች የአፈር መሸርሸርን በመከላከል ለግብርና ምርትና ምርታማነት ማደግ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው ብለዋል፡፡

ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት እየተተከሉ መሆኑን ጠቁመው÷ ይህም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተያዘው ሀገራዊ ግብ እውን እንዲሆን ዓይነተኛ ሚና እንደሚጫወት መጥቀሳቸውን ኢዜአ ነው የዘገበው፡፡

“በመትከል ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ ዘንድሮ እየተከናወነ ለሚገኘው ሰባተኛ ዙር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ስኬት ሁሉም የበኩሉን አሻራ እንዲያኖር ጥሪ አቅርበዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.