Fana: At a Speed of Life!

ማሰልጠኛ ማዕከሉ ከብልጽግና ጉዟችን ጋር አብሮ የሚራመድ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት የቢሾፍቱ ማሰልጠኛ ማዕከል ከብልጽግና ጉዟችን ጋር አብሮ የሚራመድ ነው አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን የማሰልጠኛ ማዕከሉን የግንባታ ፕሮጀክቶች፣ የስልጠና ክፍሎችን እና የስልጠና ማዕከሉን የሥራ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅትም ኢንስቲትዩቱ ለረጅም ዓመታት የመንግስትና የግል ዘርፉን በየደረጃው ያሉ አመራሮች እና ሙያተኞችን አቅም በመገንባትና በማብቃት ለበርካታ ዓመታት ጉልህ አሻራውን አሳርፏል ብለዋል።

የመንግሥት አገልግሎት እና አስተዳደርን ለማሻሻል የተጀመረውን ሪፎርም በመደገፍ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ የሚገኝ ተቋም እንደሆነም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

የቢሾፍቱ ማሰልጠኛ ማዕከል ለበርካታ ተቋማት ስልጠና በመስጠት፣ በማማከር እና በዘርፉ ምርምር በማድረግ ላይ የሚገኝ ውብ የአረንጓዴ ገጽታ እና ሰፊ ግቢ እንዳለው ጠቅሰዋል፡፡

ማዕከሉ ከብልፅግና ጉዟችን ጋር አብሮ የሚራመድ ብቻ ሳይሆን የመንግስትን እና የግል ዘርፉን ተቋማዊ ለውጥ እና የመፈፀም አቅም ለማጎልበት የለውጥ አርዓያ መሆን አለበት ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡

ሀገራዊ መሻትን ያገናዘቡ፣ በሰልጣኞች ዘንድ እውቀትን፣ ሀሴትን እና የለውጥ ቁጭትን የሚፈጥሩ ምቹ የማሰልጠኛ፣ የሰልጣኞች ማደሪያና የመዝናኛ ክፍሎችን እንዲገነባም አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

የፌደራል መንግሥት የሥልጠና ማዕከሉን ለማዘመን አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.