Fana: At a Speed of Life!

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 51 ነጥብ 6 ሚሊየን ኩንታል ምርት ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ2017 በጀት ዓመት ከመኸር አዝመራ 51 ነጥብ 6 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ተሰበሰበ፡፡

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባዔ በወልቂጤ ከተማ እየተካሔደ ነው፡፡

የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በም/ቤቱ የቀረበውን የ2017 በጀት የግብርና አፈጻጸም አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ÷በዓመቱ የዘርፉን ምርታማነት ለማሳደግ የተለያዩ ንቅናቄዎችን በመተግበር በርካታ ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል፡፡

በክልሉ ዘመኑን የዋጁ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በተከናወኑ ሥራዎችም ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ ያደረጉ ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል ነው ያሉት፡፡

‎‎በመኸር እርሻ 559 ሺህ 592 ሔክታር መሬት በማልማት ከ51 ነጥብ 6 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን ሃላፊው ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

በዘርፉ ከላይኛው አመራር እስከ አርሶ አደሩ የተደረገው ክትትልና ድጋፍ ለውጤታማነቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን አመልክተዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም አርሶ አደሩ ሜካናይዜሽንን እንዲያስፋፋ እና የግብዓት አቅርቦት በወቅቱ እንዲያገኝ በትኩረት መሰራቱን ነው ያስረዱት፡፡

በተለይም የአፈር ማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር በሁሉም አካባቢዎች በሚፈለገው መጠን በወቅቱ ተደራሽ መደረጉን አብራርተዋል፡፡

በክልሉ በሌማት ትሩፋት፣ በመስኖ ልማትና ሌሎች ንቅናቄዎች የሕብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ተጨባጭ ውጤቶች መገኘታቸውን አስገንዝበዋል፡፡

በቀጣይም በአርሶ አደሩ ዘንድ የተፈጠረውን አዲስ የሥራ ባህል በማጠናከር ምርታማነቱን እንዲያሳድግና ሕይወቱን እንዲያሻስል በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.