Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት ምክትል ዋና ጸሃፊ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት ምክትል ዋና ጸሃፊ አሚና መሃመድ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ ኢትዮጵያ ለመጪዎቹ ሶስት ቀናት በአዲስ አበባ የሚከናወነውን 2ኛውን የተባበሩት መንግሥታት የምግብ ሥርዓት ጉባዔ በጋራ በማዘጋጀቷ ኩራት ይሰማታል ብለዋል።

ዛሬ ማለዳም የተባበሩት መንግሥታት ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሃመድን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው ማነጋገራቸውን ተናግረዋል፡፡

በውይይታቸው በመላው አፍሪካና በተቀረውም ዓለም ዘላቂ፣ አካታችና በተለያዩ ፈተናዎች የማይበገር የምግብ ሥርዓት አስፈላጊነትን ጨምሮ በሌሎች ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል፡፡

ኢትዮጵያ በተቀናጁ ፖሊሲዎቿ፣ ለአየር ንብረት ጥበቃ ምላሽ ሰጪ በሆነ የግብርና ሥራዋ ብሎም በምግብ ዋስትና እና ለሁሉም የተመጣጠነ ምግብ በማቅረብ ማኅበረሰብ መር ዘዴዎቿ የምግብ ሥርዓትን ለማሻሻል ባላት ጽኑ አቋምና ተግባር ቀጥላለች ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.