Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼህ መሃሙድ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼህ መሃሙድ ጋር ተወያዩ፡፡

ኢትዮጵያ በክብር በምታስተናግደው የ2ኛው የተባበሩት መንግሥታት የምግብ ሥርዓቶች ጉባኤ እንኳን በደህና መጡ ሲሉም ለፕሬዚዳንቱ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ የትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፥ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ጥልቅ መሠረት ያለው ታሪካዊ፣ ባሕላዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ትስስርን የሚጋሩ ሀገራት መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ይህንን የሀገራቱን ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር መሥራታቻንን እንቀጥላለንም ነው ያሉት፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.