Fana: At a Speed of Life!

ሀገር አቀፍ የሰላም ጉባኤ በሐረር ከተማ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሚያዘጋጀው አራተኛው ሀገር አቀፍ የሰላም ጉባኤ በሐረር ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

ጉባኤው ሃይማኖት ለሰላም፣ አንድነትና አብሮነት ላይ እየመከረ ሲሆን÷ የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ኃላፊዎች እና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍል ተወካዮች ተገኝተዋል።

ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት የሚካሄደው የሰላም ጉባኤ በሀገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም ተገልጿል።

ጉባኤው ከዚህ ቀደም በድሬዳዋ፣ ጅማ እና ባሕር ዳር በተካሄዱ የሰላም ጉባኤዎች ሕብረተሰቡ የሰላም ባለቤት እንዲሆን የሚያስችሉ ተግባራት መከናወናቸውም ተመላክቷል።

በጌታሰው የሽዋስ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.