Fana: At a Speed of Life!

የባህር በር የሌላቸው በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን በተመለከተ የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ያነሷቸው ዋና ዋና ሀሳቦች፡-

👉 የባህር በር የሌላቸው በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት የዓለምን 7 በመቶ ህዝብ ይወክላሉ
👉 ኢፍትሃዊ የሆነው የዓለም የንግድ ስርዓት እነዚህን ሀገራት ያገለለ ነው
👉 ሀገራቱ ለከፍተኛ የትራንስፖርት ወጪ ተዳርገዋል፤ የንግድ ተሳትፏቸው ተገድቧል
👉 ተገማች ላልሆነው የዓለም የሸቀጦች ዋጋ ተጋላጭ ሆነዋል
👉 በውስን የኢኮኖሚ መሰረት ላይ እንዲቆዩ ተገድደዋል
👉 የሀገራቱ ስኬት ለአጀንዳ 2030 መሳካት ወሳኝ ነው
አንቶኒዮ ጉተሬዝ ሊታረሙ ይገባል በማለት ያነሷቸው ሀሳቦች፡-
🔹የባህር በር አልባ መሆን የሀገራትን እጣፈንታ ሊወስን አይገባም
🔹ሀገራቱ እየተጋፈጡት ያለውን ኢፍትሃዊ የንግድ ስርዓት በአፋጣኝ ማሻሻል ያሻል
🔹በሀገራቱ የመልማት እድሎች ላይ የተጋረጡትን ገደቦች ማንሳት ያስፈልጋል
በቀጣይ አስር ዓመታት መስራት ይጠበቅብናል ያሏቸው 4 መሰረታዊ ጉዳዮች፥
▪️ መዋቅራዊ ለውጥና ብዙሃንን ያማከለ ኢኮኖሚን ገቢራዊ ማድረግ
▪️ ንግድንና ቀጣናዊ ትስስርን ማጠናከር
▪️ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን የመቋቋም ጥረቶችን ማጠናከር
▪️ ለሀገራቱ የፋይናንስ ድጋፍና አጋርነትን ማጠናከር
🔹 የተባበሩት መንግስታት የባህር በር የሌላቸው በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን የፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጥያቄና ጥረት በመደገፍ ከሀገራቱ ጎን ይቆማል
በኃይለማርያም ተገኝ
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.