ለኢንተርፕራይዞች ከ18 ቢሊየን ብር በላይ ብድር ተሰራጨ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመት ለአምራች ኢንተርፕራይዞች ከ18 ቢሊየን ብር በላይ የሥራ ማስኬጃ ብድርና የማምረቻ መሳሪያ ተሰራጭቷል፡፡
የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ጳውሎስ በርጋ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ ኢንተርፕራይዞች ከብድርና መስሪያ ቦታ ጋር በተያያዘ የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች ለመፍታት እየተሰራ ነው፡፡
በተለይም የዘርፉን አሰራር ሥርዓት ለማሻሻል፣ የማምረት አቅምን ለማሳደግና ጥራት ያለው ምርት ለማምረት በቁርጠኝነት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ለአምራች ዘርፉ ልዩ ትኩረት መስጠቱን የተናገሩት ም/ዋና ዳይሬክተሩ ÷ በዚህም አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝ አንስተዋል፡፡
በ2017 በጀት ዓመት ለ1 ሺህ 740 አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች 11 ነጥብ 38 ሚሊየን ብር በላይ የሥራ ማስኬጃ ብድር መሰራጨቱን ጠቁመዋል፡፡
እንዲሁም ለ1 ሺህ 462 አምራች ኢንተርፕራይዞች 6 ነጥብ 99 ቢሊየን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የማምረቻ መሳሪያዎች ተሰራጭተዋል ነው ያሉት፡፡
በቀጣዩ ዓመት ለኢንተርፕራይዞች የብድር አቅርቦትና የማምረቻ ቦታ ተደራሽነትን ለማስፋት በትኩረት እንደሚሰራም አመልክተዋል፡፡
በመላኩ ገድፍ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!