በኦሮሚያ ክልል በ14 ዘርፎች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተከናወነ ነው
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል በ14 ዘርፎች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተጠናከረ መልኩ እየተከናወነ ነው አለ የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ።
በቢሮው የወጣቶች በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ዳይሬክተር አቶ አሚኖ አማን እንዳሉት÷የዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች እየተከናወነ ይገኛል።
ለመርሐ ግብሩ ስኬታማነት ከክልል ጀምሮ በየደረጃው ባለው መዋቅር ቅንጅት መፈጠሩን ጠቁመው÷ለዚህም በርካታ ወጣቶችን በማንቀሳቀስ ሕዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
አገልግሎቱ በ14 ዘርፎችና በ35 የሥራ ዝርዝሮች ላይ በማተኮር እየተከናወነ ሲሆን÷ ዘርፎቹ የሕዝቡን ኑሮ የሚያሻሽሉ እና ዘላቂ ልማትን ለማረጋገጥ እንደሚያግዙ ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡
በተለይም በአረንጓዴ አሻራ፣ በደም ልገሳ፣ የአቅመ ደካሞች ቤት እድሳትና ግንባታ፣ በሰላም ግንባታ እና ሌሎች ሥራዎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ እየተከናወነ እንደሚገኝ አመልክተዋል፡፡
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!