ግብርናውን የሚያዘምኑ ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሀገር ለማስገባት እየተሰራ ነው
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የምግብ ፍጆታዋን ለማሟላት ግብርናውን የሚያዘምኑ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ወደ ሀገር ለማስገባት እየሰራች ነው፡፡
የናሽናል ኤርወይስ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ገዘሀኝ ብሩ እንዳሉት፤ በቅርቡ በግብርና ሚኒስቴር ወደ ሀገር ውስጥ የገቡት የኬሚካል ርጭት ዘመናዊ አውሮፕላኖች ግብርናውን ወደኋላ የጎተተውን የኬሚካል ርጭት ያዘምናሉ።
ዘመናዊ አውሮፕላኖቹ ግብርናውን ለማሳደግ እየተደረገ ያለው ጥረት አንድ አካል መሆኑን ጠቅሰው፤ አርሶ አደሩ በአረም እና በተባይ አማካኝነት የሚያጋጥመውን የምርት መቀነስ ችግር እንደሚፈታ ተናግረዋል።
አውሮፕላኖቹን መጠቀም ምርታማነትን ከመጨመርም ባለፈ በኋላቀር ርጭት አማካኝነት የሚከሰቱ ችግሮችን በመፍታት አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።
አውሮፕላኖቹ ሰፋፊ እርሻዎችን ተደራሽ ለማድረግ እጅግ ወሳኝ ናቸው ብለዋል።
አውሮፕላኖቹ አገልግሎት የሰጡባቸው ወረዳዎች ባለሙያዎች እና አርሶ አደሮች እንዳመለከቱት፤ ለኬሚካል ርጭት ይባክን የነበረውን ጉልበት እና ጊዜ ማስቀረት ተችሏል።
በጥላሁን ይልማ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!