የዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ከፕሬዚዳንት ፑቲን ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ማስቆም በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ ሁለቱ ወገኖች ጦርነቱን ማስቆም በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ሀሳብ መለዋወጣቸውን ገልጸዋል፡፡
ልዩ መልዕክተኛው ከፕሬዚዳንት ፑቲን ጋር የነበራቸውን ውይይት ለፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ካደረሱ በኋላ በዋሽንግተን እና ሞስኮ መካከል ተጨማሪ ድርድሮች እንደሚደረጉ ጠቁመዋል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ10 ቀናት ውስጥ ሩሲያ እና ዩክሬን ተኩስ አቁም እንዲያደርጉ ቀነ ገደብ በመስጠት ሩሲያ የማትስማማ ከሆነ በሞስኮና በነዳጅ ግብይት ሼሪኮቿ ላይ ማዕቀብ እንደሚጥሉ ማሳሰባቸውም ይታወሳል፡፡
በኔቶ የአሜሪካ አምባሳደር ማቲው ዊትከር የልዩ መልዕክተኛው ጉብኝት የሩሲያ እና ዩክሬንን ጦርነት ሊያስቆም እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ መግለፃቸውን ቢቢሲ እና አር ቲ ዘግበዋል፡፡
በሚኪያስ አየለ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!