ለኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞ ስኬታማነት ሰላምን ማጽናት…
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለኢትዮጵያ የማንሰራራት ጉዞ ስኬታማነት ሰላምን ማጽናት የሁሉም ኃላፊነት መሆን አለበት አሉ የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ።
በሰላም ሚኒስቴር አዘጋጅነት ከሁሉም ክልሎች እና ከሁለቱ የከተማ አስተዳደር የተወጣጡ የሰላምና ጸጥታ ዘርፍ አመራሮች በአዳማ ያካሄዱት የምክክር መድረክ ተጠናቋል።
በማጠቃለያ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የሰላም ሚኒስትሩ ሰላምን እና ልማትን በማቀናጀት መተግበር ይገባል ብለዋል።
ለሀገር ግንባታ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባ ጠቁመው÷ የሀገርን ከፍታ ለማረጋገጥ በሁሉም ዘርፎች ቅንጅታዊ አሰራር ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
የሃይማኖት ተቋማት ለሰላም ግንባታ ያላቸውን ከፍተኛ ሚና ለመጠቀም እየተሰራ መሆኑን ገልጸው÷ ባህላዊ የችግር አፈታት ስርዓቶችን ለሀገር ግንባታ የመጠቀም ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ለመጪው ትውልድ ሁለንተናዊ ብልጽግናዋ የተረጋገጠ ሀገር ለማስረከብ እየተሰራ እንደሆነ መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!