በሀረር ከተማ በታቀደላቸው ጊዜና ጥራት እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶች…
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሀረር ከተማ የቱሪዝም ዘርፉን የሚያሳድጉና የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ፕሮጀክቶች እየተሰሩ ናቸው አሉ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ።
አቶ ኦርዲን በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ የአባድር ፕላዛ፣ የሀረር ላንድ ማርክ የኮሪደር ልማት፣ የመሶብ አንድ ማዕከል፣ የሀማሬሳና ኢኮፓርክ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
በጉብኝታቸውም በክልሉ እየተከናወኑ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በታቀደላቸው ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል።
በተለይም በሀረር ከተማ እየተሰሩ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶች የከተማውን እድገት የሚያፋጥኑ፣ የቱሪዝም ዘርፉን የሚያሳድጉና የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያግዙ ናቸው ብለዋል።
ፕሮጅቶቹ ተቋማዊ የመፈፀም አቅም፣ ቅንጅትና ቁርጠኝነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበተ መምጣቱ በተግባር የታየበት መሆኑን አቶ ኦርዲን አንስተዋል።
ህዝብን ባሳተፈ መልኩ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ስራዎች የሀረርን የማንሰራራት ዘመን እውን ለማድረግ ከማስቻል ባሻገር ለዜጎች የስራ እድል በመፍጠር ረገድ ጉልህ ሚና እያበረከቱ መሆናቸውንም ነው የተናገሩት።
በቀጣይም ጥራትና ፍጥነትን መሰረት ባደረገ መልኩ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ፕሮጀክቶችን የማጠናቀቅ ስራ ይሰራል ብለዋል።
በተስፋዬ ኃይሉ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!