Fana: At a Speed of Life!

ለውጭ ገበያ ከቀረበ ዕጣን ከ1 ነጥብ 6 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለውጭ ገበያ ከቀረበ የዕጣን ምርት ከ1 ነጥብ 6 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።

የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የኮሙኒኬሽንና ማኅበራዊ ኃላፊነት ሥራ አመራር ሥራ አስኪያጅ ጋሻው አይችሉህም 2 ሺህ 505 ኩንታል ዕጣን ወደ ቻይና፣ ዱባይ፣ ግሪክ፣ ቱኒዝያና ቱርክ በመላክ ከ1 ሚሊየን 641 ሺህ ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ተናግረዋል፡፡

260 ኩንታል ዕጣን ለሀገር ውስጥ ገበያ በማቅረብ ከ7 ሚሊየን 710 ሺህ ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸው÷ በዚህም የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለው አንስተዋል፡፡

ኮርፖሬሽኑ ከሚሰበስበው የዕጣን ምርት ከ90 በመቶ በላይ ያህሉን ለውጭ ገበያ እንደሚያቀርብ ጠቁመዋል።

በዘርፉ የሚስተዋል ሕገወጥ ንግድ እና ሌሎች ተግዳሮቶች ሀገሪቱ ከተፈጥሮ ሙጫና ዕጣን ሽያጭ በሚፈለገው ልክ ተጠቃሚ እንዳትሆን ማድረጉን አመላክተዋል፡፡

በ2018 በጀት ዓመት 2 ሺህ 510 ኩንታል የዕጣን ምርት ወደ ውጭ በመላክ ከዘርፉ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ ለማሳደግ ታቅዷል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.