ከወረቀት ንክኪ ነጻ የሆነ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ቴክኖሎጂ ተመረቀ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያበለጸገው ከወረቀት ንክኪ ነጻ የሆነ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ቴክኖሎጂ በዛሬው ዕለት ተመርቋል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ ቴክኖሎጂው የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ቀልጣፋና ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡
አሁን ላይም ቴክኖሎጂው በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት፣ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እና በፕላንና ልማት ሚኒስቴር እየተተገበረ ይገኛል ብለዋል፡፡
በቀጣይ ወደ ሌሎች ተቋማት እና ክልሎች የማስፋፋቱ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው ሚኒስትሩ ያስገነዘቡት፡፡
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) በበኩላቸው ÷ ቴክኖሎጂው ኮሚሽኑ እያከናወናቸው ለሚገኙ የሪፎርም ሥራዎች ትግበራ አጋዥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የመንግስትን አገልግሎት በማቀላጠፍ የዜጎችን እርካታ የሚያረጋግጥ ነው ያሉት ደግሞ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሰው ሃብት ልማት ሥምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ናቸው።
ቴክኖሎጂው ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ለተጀመረው ጥረት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተመላክቷል።
በወንድሙ አዱኛ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!