Fana: At a Speed of Life!

የትራምፕና ዘለንስኪ ውይይት በነጩ ቤተ መንግስት…

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በኋይት ሃውስ በድጋሚ ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነትን ማስቆም በሚቻልበት ሁኔታ፣ ሊኖሩ ስለሚችሉ የሰላም ጥረቶች፣ በአሜሪካ ድጋፍና ሌሎች ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ትራምፕ በዚህ ወቅት ÷በጦርነቱ የሰዎችን ሞት ለማስቀረት የተኩስ አቁም ሃሳብን እንደሚደግፉ ተናግረዋል፡፡

ይሁን እንጂ ለአንድ ወገን ብቻ ስልታዊ ጥቅም በማይሆን መልኩ መደረግ እንዳለበት ነው አጽንኦት የሰጡት፡፡

“እኛ ሰላም ለማምጣት እየሰራን ነው” ያሉት ፕሬዚዳንት ትራምፕ÷ ለአጭር ጊዜ የተኩስ አቁም ሳይሆን ሰፊና ዘላቂ የሰላም ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚገባ አስረድተዋል።

ቮሎድሚር ዘለንስኪ በበኩላቸው÷ ዩክሬን ጦርነቱን ለማቆም “ዲፕሎማሲያዊ መንገድ” ለመፈለግ ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።

በዮናስ ጌትነት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.