Fana: At a Speed of Life!

የጌደብ ወንዝ ድልድይ ነገ ለተሽከርካሪ ክፍት ይሆናል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከደብረ ማርቆስ – ባሕርዳር በሚወስደው መንገድ የሚገኘው የጌደብ ወንዝ ድልድይ በነገው ዕለት ለተሽከርካሪ ክፍት ይደረጋል አለ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር፡፡

አስተዳደሩ ለፋና ዲጂታል እንደገለጸው ÷ በጎርፍ ጉዳት ደርሶበት የነበረውን የጌደብ ወንዝ ድልድይ በተገጣጣሚ ብረት የመገንባቱ ሥራ ተጠናቅቋል፡፡

ድልድዩ ነገ ነሐሴ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ሙሉ ለሙሉ ለተሽከርካሪ ክፍት እንደሚደረግም አመልክቷል፡፡

የጌደብ ወንዝ ድልድይ ነሐሴ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ሌሊት ጮቄ ተራራ ላይ የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ በደረሰበት ጉዳት ከደብረ ማርቆስ – ባሕርዳር የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጦ መቆየቱ ይታወቃል፡፡

ድልድዩ በጎርፍ ምክንያት ጉዳት ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ ግንባታው እስኪጠናቀቅ በትዕግስት ሲጠባበቁ ለቆዩ መንገደኞችና አሽከርካሪዎች ምስጋና ቀርቧል፡፡

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.