Fana: At a Speed of Life!

የአዲስ አበባ ከተማ የገበያ ማዕከላት የንግድ ኤግዚቢሽን እና ባዛር ተከፈተ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ የገበያ ማዕከላት የንግድ ኤግዚቢሽን እና ባዛር በአራት ኪሎ ባሻ ወልዴ ችሎትና አፍሪካ ሕብረት በሚገኙት ማዕከላት በዛሬው ዕለት ተከፍቷል።

ኤግዚቢሽንና ባዛሩን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጨምሮ የከተማዋ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተከፍቷል።

የገበያ ማዕከላቱ ባዛር ለመጭው በዓል የሚሆኑ የተለያዩ ግብአቶች ቀርበውበታል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በወቅቱ እንዳሉት÷ በማዕከላቱ የተከፈተው የንግድ ኤግዚቢሽን እና ባዛር ሸማቹን ከአምራቹ ጋር በቀጥታ በማገናኘት በበዓል ወቅት የሚያጋጥመውን ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ ለመከላከል ያስችላል፡፡

በተጨማሪም የገበያ ማዕከላቱ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች የማህበረሰቡን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን የሚሳዩ ናቸው ብለዋል፡፡

ለመጭው በዓል በማዕከላቱ ከተከፈቱ ኤግዚቢሽንና ባዛሮች በተጨማሪ ለማህበረሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ የሚሸጡ ባዛሮች በሁሉም ክፍለ ከተሞች ይከፈታሉ ተብሏል፡፡

በቅድስት አባተ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.