Fana: At a Speed of Life!

በሶማሌ ክልል የጽናት ቀን ተከበረ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሶማሌ ክልል ጳጉሜን 1 የጽናት ቀን ‘ጽኑ መሰረት፤ ብርቱ ሀገር’ በሚል መሪ ቃል በጅግጅጋ ከተማ ተከብሯል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት ሃላፊ ሁሴን ቃስን (ዶ/ር) በሥነ ሥርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት÷ በፅናትና በትብብር ለሰላም ግንባታና ልማት ጠንክረን እንሰራለን ብለዋል፡፡

ለሀገራችን መጽናትና ሰላም መስፈን መስዋዕትነት የከፈሉ ጀግኖችን በማስታወስ የኢትዮጵያን ልማትና ዕድገት ማስቀጠል ይኖርብናል ነው ያሉት፡፡

ጸንተን በጋራ በመተባበር ለክልላችን ብሎም ለሀገራችን ሰላም ግንባታ፣ ልማትና ዕድገት መትጋት አለብን ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የመከላከያ ሰራዊትና የፌዴራል ፖሊስ አመራሮችን ጨምሮ ሌሎችም የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.