በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የጽናት ቀን ተከበረ
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጳጉሜን 1 የጽናት ቀን ‘ጽኑ መሠረት፤ ብርቱ ሀገር’ በሚል መሪ ቃል በአሶሳ ከተማ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ተከብሯል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታሁን አብዲሳ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በኢትዮጵያውያን የተባበረ ጥረት የተገነባው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በጽናት ለስኬት የበቃንበት ነው ብለዋል፡፡
በለውጡ ዓመታት የኢትዮጵያውያን የጽናት ማሳያዎችና በትብብር ተጨባጭ ውጤት የተመዘገበባቸው የስኬት ተምሳሌቶች መኖራቸውን ገልጸው፤ በቀጣይም ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር እና በጽናት በመሻገር ልማት በጋራ ማስቀጠል እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
በዕለቱ በማርቺንግ ባንድ የታጀበ የእግር ጉዞ የተደረገ ሲሆን የኢትዮጵያን የጽናት ማሳያዎችና የከፍታ ጉዞ የሚያወሱ የስነ ጽሁፍ ስራዎች መቅረባቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የመከላከያ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት፣ የክልሉ አመራሮችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች ተገኝተዋል።
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!