ኒውካስል፣ ቦርንማውዝ እና ፉልሃም ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ4ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ኒውካስል፣ ቦርንማውዝ እና ፉልሃም ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡
ቀን 11 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ ኒውካስል ዎልቭስን 1 ለ 0፣ ቦርንማውዝ ብራይተንን 2 ለ 1 እንዲሁም ፉልሃም ሊድስ ዩናይትድን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
ክሪስታል ፓላስ ከሰንደርላንድ እንዲሁም ኤቨርተን ከአስቶንቪላ ጋር ያደረጉት ጨዋታ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቅቋል፡፡