Fana: At a Speed of Life!

ጆዜ ሞሪኒሆ የቤኔፊካ አሰልጣኝ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪኒሆ የፖርቹጋሉ ክለብ ቤኔፊካ አሰልጣኝ መሆናቸው ይፋ ሆነ።

ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ በቤኔፊካ እስከ ፈረንጆቹ 2027 የሚያቆያቸውን የሁለት ዓመት ኮንትራት ተፈራርመዋል።

ሞሪኒሆ ከዚህ ቀደም ሪያል ማድሪድ፣ ኢንተር ሚላን፣ ቼልሲ፣ ቶተንሃም ሆትስፐር እንዲሁም ፖርቶን የመሳሰሉ ክለቦችን ማሰልጠናቸው የሚታወስ ነው።

በቅርቡ ከቱርኩ ክለብ ፌነርባቼ የተሰናበቱት አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ ወደ ኃላፊነት በመመለስ የቤኔፊካ አሰልጣኝ ሆነዋል።

አሰልጣኙ በዚህ የውድድር ዓመት በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ቤኔፊካን እየመሩ የቀድሞ ክለቦቻቸውን ቼልሲ እና ሪያል ማድሪድ የሚገጥሙ ይሆናል።

በወንድማገኝ ፀጋዬ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.