Fana: At a Speed of Life!

የጋሞ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ “ዮ ማስቃላ” በዓል እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የጋሞ ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ “ዮ ማስቃላ” በዓል በአርባምንጭ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው።

ዮ ማስቃላ በዓል በብሔረሰቡ ዘንድ ዘመን መለወጫ ብቻ ሳይሆን ያዘነን የሚያጽናና፣ የተጣላን የሚያስታርቅ፣ የተራራቀን የሚያቀራርብ ልዩ ትርጉም ያለው በዓል ነው።

በበዓሉ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ እና በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የፌደራልና ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በተጨማሪም ከተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች የተወጣጡ እንግዶች በበዓሉ ላይ ታድመዋል።

በዓሉ በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ አባያ ካምፓስ ስታዲየም ነው እየተከበረ የሚገኘው።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.