የጎፋ “ጋዜ ማስቃላ” እና የኦይዳ “ዮኦ ማስቃላ” በዓላት እየተከበሩ ነው
አዲስ አበባ፣ መስከረም 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የጎፋ ዞን ሕዝቦች የዘመን መለወጫ የጎፋ “ጋዜ ማስቃላ” እና የኦይዳ “ዮኦ ማስቃላ” በዓላት በሳውላ ከተማ በድምቀት እየተከበሩ ነው፡፡
በአከባበር ሥነ ሥርዓቱ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፣ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጂጌ (ዶ/ር) እና ሌሎች የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ታድመዋል፡፡
የጎፋ ዞን ሕዝቦች የአዲስ ዘመን ማብሰሪያ የሆኑት በዓላቱ የሰላም፣ የፍቅር፣ የአብሮነትና የአንድነት ባሕላዊ እሴቶችንና ትውፊቶችን በሚያንጸባርቁ መልኩ ነው እየተከበሩ የሚገኙት፡፡
ዘመናት በተሻገረ አብሮነት የተጋመዱና ባሕላዊ እሴቶቻቸው ተወራርሰው የተሰናሰሉት የጎፋና የኦይዳ ሕዝቦች በየራሳቸው የጊዜ ቀመር የዘመን መለወጫ በዓላት አሏቸው፡፡
የጎፋ “ጋዜ ማስቃላ” እና የኦይዳ “ዮኦ ማስቃላ” የዘመን መለወጫ በዓላትንም በወንድማማችነት እሴቶች አንድነታቸውን አጽንተው በጋራ በታላቅ ድምቀት ያከብራሉ፡፡
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!