Fana: At a Speed of Life!

የአቢሲንያ ባንክ አጠቃላይ ሀብት 286 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ደረሰ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አቢሲንያ ባንክ አጠቃላይ ሀብቱ 286 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ደረሰ።

የአቢሲንያ ባንክ ባካሄደው 29ኛ መደበኛና 16ኛ አስቸኳይ ጉባዔ የዳሬክተሮች ቦርድ ዓመታዊ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን÷ በተጠናቀቀው የሂሳብ ዓመት የባንኩ ጠቅላላ ገቢ 39 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር መድረሱን አስታውቋል።

ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ91 ነጥብ 1 በመቶ ጭማሪ ወይም 11 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ትርፍ ማስመዝገቡን አመላክቷል።

በአጠቃላይ 91 ነጥብ 4 በመቶ ጭማሪ በማሳየት 10 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱን የገለጸው ባንኩ÷ አጠቃላይ ካፒታሉም ወደ 28 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ማደጉን ገልጿል።

የባንኩ አጠቃላይ ሀብት ካለፈው ዓመት አጠቃላይ ሀብት ጋር ሲነፃፀር የ28 ነጥብ 8 በመቶ እድገት በማሳየት 286 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ደርሷልም ነው የተባለው በሪፖርቱ።

ባንኩ በዲጂታል ባንኪንግና የመረጃ ቴክኖሎጂ ግንባታ በማሳደግ 1 ሺህ 700 በላይ ኤቲኤም፣ ከ3 ሺህ 600 በላይ ፖስ እንዲሁም 49 ቨርቹዋል የባንክ አገልግሎት ማዕከል ማድረጉ ተመላክቷል።

ባንኩ ማህበራዊ ኃላፊነትን ከመወጣት አኳያ 91 ሚሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉንም ጠቁሟል።

በእየሩሳሌም አበበ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.