Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅቷን አጠናቀቀች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅቷን አጠናቅቃለች አለ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር።

የዝግጅቱ መጠናቀቅና የግብይት ማስጀመሪያ መርሐ ግብርን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴዔታ ያስሚን ወሃብረቢ የስምምነቱ ትግበራ ለኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል፡፡

የግብይት ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ መስከረም 29 ቀን 2018 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑንም ጠቁመዋል።

በዚህም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ ሥጋ፣ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በየብስ ትራንፖርት ቡና፣ የጥራጥሬ ምርቶችና የቅባት እህሎች ወደ ኬንያ፣ ሶማሊያ እና ደቡብ አፍሪካ እንደሚላክ አብራርተዋል፡፡

አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ስምምነት ትግበራ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች እንደሚኖሩት ጠቁመው÷ ለሀገር ውስጥ ንግድ ተወዳዳሪነትና ኢንቨስትመንት መነቃቃት፣ ለሸማቹ የተሻለ አማራጭና ሰፊ የምርት አቅርቦት እንዲሁም በአፍሪካ ሀገራት መካከል የገበያ ትስስርን ለማስፋት እንደሚያስችል ጠቅሰዋል፡፡

በቤተልሔም መኳንንት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.