Fana: At a Speed of Life!

የሸገር ከተማ በ12ኛ ክፍል ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ዕውቅና ሰጠ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሸገር ከተማ አስተዳደር በ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከ500 ነጥብ በላይ በማምጣት ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ዕውቅና ሰጠ።

ከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የግልና የመንግሥት ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ተማሪዎቻቸው ነው የማበረታቻ ዕውቅና የሰጠው።

የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፊራኪያ ካሣሁን የግልና የመንግሥት ትምህርት ቤቶች ውጤታማ ተማሪዎችን እንዲያፈሩ የመደገፍ ስራ እየተሰራ መሆኑን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል።

ቢሮው የትምህርት ቤቶቹን ተደራሽነት በማስፋፋት የግልና የመንግሥት ት/ቤቶች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ በመደገፍ የበኩሉን አስተዋጽዖ እየተወጣ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

በዚህም ትምህርት ቢሮ በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከ500 ነጥብ በላይ ውጤት ያስመዘገቡ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የሜዳሊያና የገንዘብ ሽልማት አበርክቶላቸዋል።

በመርሐ ግብሩ 57 ተማሪዎች የሜዳሊያ ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን÷ 6 ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ተጨማሪ የገንዘብ ማበረታቻ ተሰጥቷቸዋል።

በታሪክ አዱኛ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.