Fana: At a Speed of Life!

ደብረ ብርሃን ፋና ኤፍ ኤም 94.0 የሕዝብ ጥያቄዎችን በማስመለስ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ደብረ ብርሃን ፋና ኤፍ ኤም 94 ነጥብ 0 የሕዝብ ጥያቄዎችን በማስመለስ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው አለ የከተማ አስተዳድሩ።
ደብረ ብርሃን ፋና ኤፍ ኤም 94 ነጥብ 0 የተመሰረተበትን 12ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡
መርሐ ግብሩ ከመንግስት ተቋማትና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በቅንጅትና በትብብር የሚሰራበትን ሁኔታ ለማጠናከር ያለመ ነው፡፡
የደብረ ብርሃን ከተማ ም/ከንቲባ ወርቃለማው ኮስትሬ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ጣቢያው ለአካባቢው ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ በመሆንና ምርትና አገልግሎትን በማስተዋወቅ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው፡፡
ለከተማው ሁለንተናዊ ዕድገት ላበረከተው አስተዋጽኦ አመስግነው÷ የሕዝቦችን አንድነትና ልማት ለማረጋገጥ በትብብር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡
በጋራ በመስራታችን ተጠቃሚ ሆነናል ያሉት የንግድ ተቋማት ባለቤቶች በበኩላቸው÷ በትብብር መስራታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡
የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ዘላለም ገበየሁ ÷ ፋና ኤፍ ኤም 94 ነጥብ 0 በአካባቢው በይዘትና በሥርጭት ጥራት ተወዳጅ መሆኑን አውስተዋል፡፡
የአካባቢውን ሃብት በማስተዋወቅና የሕብረተሰብ ጥያቄዎች እንዲመለሱ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን አንስተው÷ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በአላዩ ገረመው
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.