Fana: At a Speed of Life!

የጋምቤላ ክልል ከ1 ሺህ 500 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ወደ ብሔራዊ ባንክ አስገባ ‎

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ‎የጋምቤላ ክልል ማዕድን ኤጀንሲ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ከ1 ሺህ 500 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ተደርጓል አለ፡፡

‎የኤጀንሲው ምክትል ዳይሬክተር አቶ ኤልያስ ገዳሙ እንዳሉት፤ በሩብ ዓመቱ 1 ሺህ 500 ኪሎ ግራም ወርቅ ገቢ ለማድረግ ታቅዶ ከዕቅድ በላይ ማሳካት ተችሏል።

በዚህም 1 ሺህ 588 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ ተደርጓል ብለዋል።

‎ለብሔራዊ ባንክ ገቢ የተደረገው የወርቅ መጠን ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ682 ኪሎ ግራም ብልጫ ማሳየቱ ተመላክቷል፡፡

‎በክልሉ በበጀት ዓመቱ 6 ሺህ ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ለማቅረብ እየተሰራ ስለመሆኑም አብራርተዋል፡፡

መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት ለብሔራዊ ባንክ የሚገባውን የወርቅ መጠንን ማሳደጉን ‎ገልጸው፤ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ሕገ ወጥ የወርቅ ግብይት እንዲቀንስ አድርጓል ነው ያሉት፡፡

‎በክልሉ በዋናነት በአራት ወረዳዎች የወርቅ ማዕድን እንደሚመረትም ገልጸዋል።

‎በአብዱ ሙሃመድ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.