Fana: At a Speed of Life!

ቼልሲ ኖቲንግሃም ፎረስትን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ቼልሲ ኖቲንግሃም ፎረስትን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

የሊጉ 8ኛ ሳምንት መርሐ ግብር የመጀመሪያ ጨዋታ ቼልሲ ኖቲንግሃም ፎረስትን በሜዳው እና በደጋፊው ፊት ነው ያሸነፈው።

በመጀመሪያው የጨዋታ አጋማሽ ምንም ግብ ማስቆጠር ያልቻሉት ቼልሲዎች በሁለተኛው አጋማሽ ሁለት ተጫዋቾችን በመቀየርና በጨዋታው ብልጫ በመውሰድ 3 ነጥብ አሳክቷል።

በጨዋታው የቼልሲን ማሸነፊያ ግቦች ጆሽ አቼምፖንግ፣ ፔድሮ ኔቶ እና ሪስ ጀምስ አስቆጥረዋል።

የፕሪሚየር ሊጉ ጨዋታዎች ቀጥለው ሲካሄዱ በተመሳሳይ ምሽት 11፡00 ላይ ብራይተን ከኒውካስል፣ በርንሌይ ከሊድስ ዩናይትድ፣ ክሪስታል ፓላስ ከበርንማውዝ፣ ማንቼስተር ሲቲ ከኤቨርተን እና ሰንደርላንድ ከወልቭስ ሲገናኙ ምሽት 1:30 ላይ ደግሞ ፉልሃም ከአርሰናል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.