Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን እና ሰንበርድ ባዮ ፊውል በአቪዬሽን ነዳጅ ልማት በትብብር ለመስራት ተፈራረሙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን እና የእንግሊዙ ኩባንያ ሰንበርድ ባዮ ፊውል አፍሪካ በታዳሽ ኃይል ዘርፍ በትብብር ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን የኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸው እና የሰንበርድ ባዮ ፊውል አፍሪካ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሪቻርድ ቤኔት ተፈራርመዋል።

በስምምነቱ መሰረት ኮርፖሬሽኑ በታዳሽ ኃይል ዘርፍ በተለይም በአቪዬሽን ነዳጅ ልማት ከሰንበርድ ባዮ ፊውል አፍሪካ ጋር በትበብር የሚሰራ ይሆናል።

አቶ ቴዎድሮስ በወቅቱ እንዳሉት፥ በኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት የተጀመሩ ሥራዎች አበረታች ውጤት እያስመዘገቡ ነው።

የዛሬው ስምምነትም የታዳሽ ኃይል፣ አረንጓዴ ልማት፣ አቪዬሽን ነዳጅ እና ሌሎች የባዮ ኢነርጂ ዘርፎችን ለማጠናከር ያስችላል ነው ያሉት።

በኢትዮጵያ የሚገኙ የተፈጥሮ ሃብቶችን በሚገባ በመለየት ጥቅም ላይ ለማዋል በትኩረት እንደሚሰራም አመልክተዋል።

ሪቻርድ ቤኔት በበኩላቸው፥ ሰንበርድ ባዮ ፊውል በተለያዩ ሀገራት በዘርፉ ያካበተውን ልምድ በመጠቀም በኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.