Fana: At a Speed of Life!

ሀዋሳ ከተማ እና ሸገር ከተማ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ4ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ እና ሸገር ከተማ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል።

ቀን 10 ሰዓት ላይ አዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሸገር ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 1 ለ 0 አሸንፏል።

ያሬድ መኮንን በ46ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠራት ግብ ነው ሸገር ከተማ ሦስት ነጥብ ይዞ መውጣት የቻለው፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ መቐለ 70 እንደርታን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

የሀዋሳ ከተማን ማሸነፊያ ግቦች ጌታነህ ከበደ (2) እና ያሬድ ብሩክ ሲያስቆጥሩ÷ የመቐለ 70 እንደርታን ብቸኛ ግብ ደግሞ ሱሌማን ሀሚድ ከመረብ አሳርፏል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.